ክፍል ሦስት
“ራሱን ሰጠ”
“ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ
ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ” ገላ 1፥4
አሁን የሚለው የጊዜ ቀመር ስያሜ ቀጣይ የሆነ የሕይወት ዑደት ማኅተም ነው:: እኔ አሁን የሚለውን ቃል ለመጻፍ ስጀምር አሁን ነበር:: ስላለፍኩት ደግሞ ቅድም ሆኗል:: የአሁኑ አሁን ቅድም የሚለውን ቃል ለመጻፍ ነው ያገለገለኝ:: መጽሐፍ ቅዱስ መለኮታዊ እስትንፋስ እንደመሆኑ አጠቃላይ መልዕክቱ ከጊዜ አንጻር ሲተመን አሁን በተባለው ጊዜ ላይ ልዩ ትኩረት አለው:: ዛሬ ሃያ አራት ሰዓታትን ሲይዝ አሁን ግን ያለንበትን ቅጽበት ብቻ የሚወክል ነው:: ባለፈውና በሚመጣው ቅጽበት መካከል ያለች ሰዓት የማንነታችን ልዩ መገለጫ ናት::
በሕይወት ውጣ ውረድ ውስጥ
የሚፈራረቁ አዎንታዊና አሉታዊ ነገሮች ሁሉ እየተከሰቱ የሚያልፉት ቅድም፣አሁንና ኋላ
በተባሉት የጊዜ ሰንሰለታማ ሂደት ውስጥ ነው ፡፡ሐዋርያው ቅድም የነበርንበት፣ አሁን ያለንበትና ጌታ ቢፈቅድ በኋላ የምንኖርበት
ይህ ዓለም ክፉ እንደሆነ ይገልጻል:: የአሁኑ ዓለም መልካምና ክፉ ነገር ሊከናወንበት ይችላል:: አዲሱ ሰው ክርስቶስን ለብሰው
እርሱ ውበት መልክ የሆናቸው ሁሉ መልካሙን ያደርጋሉ:: አንድ ጊዜ በክርስቶስ ስለጸደቁ ራሳቸውን የክፉ ነገር ባርያ አያደርጉም
የክርስቶ ልብ አላቸውና :: ከክርስቶስ
ውጭ ያሉት ደግሞ ክፉን ያደርጋሉ:: የክፉ ድርጊት መነሻው በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ አለማመን ነው:: የአሁኑ ዓለም ተብሎ የተገለጸው
የዕለትተዕለት የሰው ኑሮ /ሕይወት/ ነው:: የዓለም ክፋ የሚገለጠው በሰው ኑሮ ውስጥ ነውና::አሁን የሚለው የጊዜ ቀመር ስያሜ ቀጣይ የሆነ የሕይወት ዑደት ማኅተም ነው:: እኔ አሁን የሚለውን ቃል ለመጻፍ ስጀምር አሁን ነበር:: ስላለፍኩት ደግሞ ቅድም ሆኗል:: የአሁኑ አሁን ቅድም የሚለውን ቃል ለመጻፍ ነው ያገለገለኝ:: መጽሐፍ ቅዱስ መለኮታዊ እስትንፋስ እንደመሆኑ አጠቃላይ መልዕክቱ ከጊዜ አንጻር ሲተመን አሁን በተባለው ጊዜ ላይ ልዩ ትኩረት አለው:: ዛሬ ሃያ አራት ሰዓታትን ሲይዝ አሁን ግን ያለንበትን ቅጽበት ብቻ የሚወክል ነው:: ባለፈውና በሚመጣው ቅጽበት መካከል ያለች ሰዓት የማንነታችን ልዩ መገለጫ ናት::
ዓለም ክፉ የተባለበት ምክንያት
ገዥውም ክፉ ስለሆነው ነው:: እርሱ ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ በሰው ማንነት ውስጥ የገባውን የክፋት አስተሳሰብና አመለካከት እንዲሁም የክፋት ስሜት እየተጠቀመ
የዓለምን ሥርዓት በነውር ሥራዎች እየመላ ብዙዎችን ለዘላለም ጥፋት ያሚመራ ነው፡፡ “ዓለምም በሞላው በክፉ እንደተያዘ እናውቃለን”
1ዮሐ 5፥19:: እንዲሁም “የዚህዓለም አምላክ የማያምኑትን ሐሳብ አሳወረ” ተብሏል:: 2ቆሮ 4፥4:: የዚህ ዓለም አምላክ የተባለው
ዲያብሎስ ነው:: እርሱ ደግሞ ሰው የልቡናው ዐይን እንዳይበራና የተደረገለትን መዳን እንዳይረዳ ይፈትናል፤ ያደርጋልም:: ከክርስቶስ
መንግሥት ውጭ ያሉ በዲያብሎስ ግዛት ውስጥ የሚኖሩ ብዙዎች በራሳቸው ክበብ ውስጥ የሐሰት ሰላምና ፍቅር አላቸው:: ጌታም ይህን ለማስረዳት እኔ የምሰጣችሁ ሰላም ዓለም እንደሚሰጣችሁ
አይደለም ብሏል:: እንዲሁም “ዓለም የራሱ የሆነውን ይወዳል” ብሏል:: የተረጋጋ የሚመስል ኑሮና መተሳሰብ ያለበት የሚመስል ፍቅር
በብዙ ዓለማውያን ዘንድ ሊታይ ይችላል:: ግን ሁሉም ሐሰት ነው::
እንግዲህ ሐዋርያው ይህን
እውነት ለማስረዳት የአሁኑን ዓለም ኑሮ/ ሕይወት/ ክፉ መሆኑን አስገንዝቧል:: ደግሞም የአሁኑ ዓለም አለ እንጂ ዓለም አላለም::
ምክንያቱም ክርስቲያኖች ተስፋ የምናደርገውና ክፉው የማይሰለጥንበት እውነተኛው ጌታ ብቻ የሚመራውና የሚያስተዳድረው ዓለም ስላለ ከመጪው ዓለም ለመለየት የአሁኑ ዓለም ብሏል::
በርግጥ የአሁኑ ዓለም ምንም
እንኳ በክፉ ቢያዝም በክርስቶስ ላሉት ግን የሥራ ቦታ ነው:: ስለዚህም ነው ሐዋርያው “በሥጋ መኖሬ ለእኔ የሥራ ፍሬ ቢሆን ምን
እንድመርጥ አላስታውቅም:: በእነዚህ በሁለቱ እጨነቃለሁ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፤ ከሁሉም ይልቅ እጅግ የሚሻል
ነውና:: ነገር ግን በሥጋ መኖሬ ስለ እናንተ እጅግ የሚያስፈልግ ነው:: ያለው:: ፊል 1፥22::